ሳምሰንግ በሽያጭ ሲመራ፣ አፕል ቦታውን ለሁዋዌ አስረክቧል
ታዋቂው የቻይና ኩባንያ ሁዋዌ በአለማችን የስማርት ሞባይል ቀፎዎች ገበያ በርካታ ምርቶችን በመሸጥ በአፕል ተይዞ የቆየውን የ2ኛነት ደረጃ መረከቡን ሲኤንቢሲ ኒውስ ዘግቧል፡፡
የቻይናው ሁዋዌ እስካለፈው ሰኔ በነበሩት ሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ በአለማቀፍ ደረጃ 54.2 ሚሊዮን ሞባይሎችን መሸጡንና በአለማቀፍ ገበያ ውስጥ የ15.8 በመቶ ድርሻን መያዙን የጠቆመው ዘገባው፤ የታዋቂው አይፎን አምራች የሆነው አፕል ኩባንያ በአንጻሩ 41.3 ሚሊዮን ሞባይሎችን በመሸጥ የ12.1 በመቶ የገበያ ድርሻ መያዙን አመልክቷል፡፡
የደቡብ ኮርያው ሳምሰንግ ኩባንያ በአለማቀፍ የሞባይል ሽያጭና የገበያ ድርሻ መሪነቱን ይዞ መቀጠሉን የጠቆመው ዘገባው፤ በተጠቀሱት ሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ 71.5 ሚሊዮን የተለያዩ አይነት የሞባይል ቀፎዎችን በመሸጥ በአለማቀፉ የሞባይል ገበያ ውስጥ የ20.9 በመቶ ድርሻውን መያዙን ገልጧል።
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል