የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ሃላፊ እና የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት የህዝብ ግንኙነት አደረጃጀት አማካሪ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ጌታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡
አቶ ተስፋዬ ጌታቸው የአማራ ክልል የገበያ፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ሆነው የሠሩ ሲሆን የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅ/ቤት ሃላፊ ሆነው ከተሾሙ ጥቂት ወራትን ብቻ ነበር ያስቆጠሩት፡፡
በአሜሪካን ሃገር በህክምና ላይ ሣሉ ህይወታቸው ያለፈው አቶ ተስፋዬ፤ በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ እንቅስቃሴ በብርቱ ይደግፉ ከነበሩ አመራሮች ተጠቃሽ እንደነበር ታውቋል፡፡
Published in
ዜና