Saturday, 21 July 2018 12:34

የጌዲኦና ጉጂ ተፈናቃዮች ቁጥር 970,000 ደርሷል ተባለ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

  በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞንና በደቡብ ክልል ጌዲኦ ዞን ካለፈው ሚያዝያ ወር አንስቶ በተቀሰቀሱ ግጭቶች ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር 970 ሺህ ያህል መድረሱን አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት ትናንት ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በተከሰቱ ግጭቶች ከደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልል ጌዲኦ ዞን 822 ሺህ 187፣ ከኦሮምያ ክልል ጉጂ ዞን ደግሞ 147 ሺህ 40 ሰዎች መፈናቀላቸውን ያስታወቀው ድርጅቱ፣ ተፈናቃዮቹ ትምህርት ቤቶችንና የመንግስት ተቋማትን ጨምሮ በተለያዩ ስፍራዎች ተጠልለው እንደሚገኙ አመልክቷል፡፡
አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት ባለፉት ግንቦትና ሰኔ ወራት ባደረገው ጥናት በመላ አገሪቱ 1.7 ሚሊዮን ዜጎች በአገር ውስጥ ተፈናቅለው እንደሚገኙና ከእነዚህም መካከል 1.2 ሚሊዮን ያህሉ በግጭት ሳቢያ የተፈናቀሉ መሆናቸውን ማረጋገጡን ዥንዋ ዘግቧል፡፡


Read 6010 times