Print this page
Monday, 16 July 2018 00:00

“የፊልም ጥበብ ማነቆዎችና የለውጥ እርምጃ” በሚል ርዕስ ውይይት ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

 የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል (ኢትዮ ፉስት) ከቫምዳስ የመዝናኛ ማዕከል ጋር በመተባበር፤ “የፊልም ጥበብ ማነቆዎችና የለውጥ እርምጃ” በሚል ርዕስ ሁለተኛውን ዙር ውይይት፤ የዛሬ ሳምንት ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ በቫምዳስ መዝናኛ ማዕከል ይካሄዳል፡፡
በውይይቱ ላይ የፊልም ባለሙያዎች፣ የሲኒማ ቤት ተወካዮች፣ ማህበራት፣ የባህልና ቱሪዝም ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉ  ሲሆን ቀደም ሲል በዘርፉ የነበሩ ማነቆዎች አሁን ባለንበት የለውጥ ዘመን እንዴት ይወገዳሉ በሚለው ላይ ጠንከር ያሉ ሃሳቦችና ጥናታዊ ወረቀቶች እንደሚቀርቡ የኢትዮፉስት መስራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ይርጋሸዋ ተሾመ ገልፀዋል፡፡ የዛሬ ሳምንት በሚካሄደው ውይይት፤ በክፍል አንድ ውይይት ላይ ለተነሱ የዘርፉ ችግሮች የመፍትሄ ሃሳቦች ይቀርባሉ ተብሏል፡፡


Read 3922 times