በደራሲ ሳምሶን ከፍያለው የተደረሱ አምስት አጫጭር ልቦለድ ታሪኮችን ያካተተው “መወልወያ አዟሪው እና ሌሎችም” መፅሐፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መፅሐፉ “ፍቅርና ንፋስ፣ “ጠርጣራው ደምሴ”፣ “ዣንጥላው ስር ሆነን”፣ “ልጅ‘ኮነሽ” እና “መወልወያ አዟሪው” የተሰኙ ከዕለት ተዕለት ህይወታችን ጋር የተቆራኙ ማህበራዊ ጉዳዮች የተዳሰሱባቸው ታሪኮች ተካትተውበታል፡፡
የደራሲው ሶስተኛ ስራ የሆነው ይሄው መፅሐፍ፤ በ140 ገፆች ተቀንብቦ፣ በ70 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን ደራሲው ከዚህ ቀደም “እንባና ትውስታ” እና “ከእለታት አንድ ቀን” የተሰኙ የአጭር ልቦለድና የግጥም መፅሐፎችን ለንባብ ማብቃቱ አይዘነጋም፡፡