የደራሲ ነጋሽ ሀሰን “የካድሬው ንስሀ” የተሰኘ መፅሐፍ ትላንት ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ ደራሲያን የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ተመረቀ መፅሐፉ በአራት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን ደራሲው በህይወታቸው ያለፏቸውን፣ እየኖሩ ያለበትንና ወደፊት ሊኖሩበት የሚመኙትን ፖለቲካዊና ማህበራዊና ምናባዊ እውነታዎችን ያካተቱባቸው እንሆኑ ደራሲው በመግቢያቸው አስፍረዋል፡፡
በ160 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ በ80 ብርና በ22 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡