Saturday, 14 July 2018 11:53

የኤርትራ ኤምባሲ ከ20 አመታት በኋላ ነገ ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የኢትዮ-ኤርትራን ግጭትና የሁለቱን አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መቋረጥ ተከትሎ በግንቦት ወር 1990ዓ.ም የተዘጋው የቀድሞው የኤርትራ ኤምባሲ ከ20 አመታት ያህል በኋላ ነገ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በተገኙበት በይፋ እንደሚከፈት ይጠበቃል፡፡
ከአዲስአበባ ስቴዲየም ፊት ለፊት የሚገኘው የቀድሞው የኤርትራ ኤምባሲ አስፈላጊው እድሳት እንደተደረገለትና ሁለቱ አገራት ባለፈው ሳምንት ባደረጉት ስምምነት መሰረት በይፋ ተከፍቶ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሚንስትር አቶ አህመድ ሽዴ ትናንትበሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ እያደረጉት ያለውንና ዛሬ የተጀመረውን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመልክተው አቶ አህመድ በሰጡት በዚሁ መግለጫ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ባለፈው ሳምንት በኤርትራ ባደረጉት ጉብኝት ሁለቱ አገራት ከተስማሙባቸው ጉዳዮች መካከል፣ ኤምባሲዎቻቸውን መልሶ መክፈት፣ የአየርትራንስፖርት እና የስልክ ግንኙነቶችን እንደገናማስጀመር የሚሉት እንደሚገኙበትም አቶአህመድ ሽዴ አስታውሰዋል።

Read 7329 times