በአለኸኝ ብርሃኔ ተደርሶ በተስፋዬ ገ/ማሪያም የተዘጋጀው “ምስጢሩ” የተሰኘ ቴአትር ዛሬ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በብሔዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡ በዚህ የሙሉ ሰዓት አዝናኝና ቁም ነገር አዘል ቴአትር ላይ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን እንደተሳተፉበት ታውቋል፡፡
በምርቃት ሥነ - ሥርዓቱ ላይ አንጋፋ የቴአትር ባለሙያዎች፣ የባህልና ቱሪዝም ኃላፊዎች፣ የቴአትር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይታደማሉ ተብሏል፡፡