Saturday, 07 July 2018 11:46

ባለፉት 6 ወራት በሜዲትራኒያን ከ1 ሺህ በላይ ስደተኞች ሞተዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በ2018 የፈረንጆች አመት ያለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ በሊቢያ በኩል በማድረግ በሜዲትራኒያን ባህር ሲጓዙ ለሞት የተዳረጉ አፍሪካውያን ስደተኞች ቁጥር ከ1000 በላይ መድረሱን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ጽህፈት ቤት ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ በሊቢያ በኩል አድርገው ወደተለያዩ የአውሮፓ አገራት ለመግባት ሊቢያ ከደረሱ የተለያዩ የአፍሪካ አገራት ስደተኞች ውስጥ ተሳክቶላቸው ወደ አውሮፓ መግባት የቻሉት ግማሽ ያህሉ ብቻ ናቸው፡፡ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ወደ አውሮፓ ሊጓዙ አስበው ሊቢያ ከደረሱ አፍሪካውያን ስደተኞች መካከል 44 በመቶው በሊቢያ የድንበር ጠባቂዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጠቆመው ተቋሙ፤ 4.5 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውን ወይም ጠፍተው መቅረታቸውን አመልክቷል፡፡
በሳምንቱ የመጀመሪያዎቹ ሶስት ቀናት ውስጥ ብቻ ወደ አውሮፓ አገራት ለመግባት በጉዞ ላይ የነበሩ ከ200 በላይ አፍሪካውያን ስደተኞች በሜዲትራኒያን ሰምጠው መሞታቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ባለፈው ሰኔ ወር ወደ አውሮፓ ለመጓዝ አስበው ሊቢያ ከደረሱ ስደተኞች መካከል 10 በመቶው ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1634 times