Print this page
Sunday, 17 June 2018 00:00

3.2 ሚ. ዶላር የዘረፉት ናይጀሪያዊ ባለስልጣን በ14 አመት እስር ተቀጡ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ፕላቶ የተባለቺው የናይጀሪያ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የኮንግረስ አባል የሆኑት ጆሽዋ ዳሪዬ፣ በ3.2 ሚ ዶላር ዝርፊያ ተከከስሰው የ14 አመታት እስር እንደተፈረደባቸው ተዘግቧል፡፡
ባለስልጣኑ እ.ኤ.አ ከ1999 እስከ 2007 የፕላቶ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ ሆነው በሚሰሩበት ወቅት ለግዛቲቱ የአካባቢ ጥበቃ የተመደበውን 3.2 ሚሊዮን ዶላር ዘርፈው፣ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በመረጋገጡ፣ የእስር ቅጣቱ እንደተጣለባቸው ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በተመሳሳይም ታራባ የተባለቺው የናይጀሪያ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት ጆሊ ናይሜ፣ ከሁለት ሳምንታት በፊት በሙስና ተከስሰው፣ የ14 አመታት እስር እንደተፈረደባቸው ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 4165 times
Administrator

Latest from Administrator