Sunday, 10 June 2018 00:00

አዲሱ የስፔን ጠ/ ሚኒስትር 64 በመቶ ሴቶች ያሉበት ካቢኔ አዋቀሩ

Written by 
Rate this item
(0 votes)


     ለእኩልነት በቁርጠኝነት የሚሰራ መንግስት እውን እናደርጋለን የሚል አቋም የያዙት አዲሱ የስፔን ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ፤ 64 በመቶ ሴቶች ያሉበት ካቢኔ ማዋቀራቸውንና በቁልፍ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ላይ ሴቶችን መመደባቸውን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከትናንት በስቲያ ይፋ ባደረጉት የካቢኔያቸው አባላት ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት 17 አባላት መካከል አስራ አንዱ ሴቶች መሆናቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ይህም አዲሱን ካቢኔ ባለፉት 45 አመታት የስፔን ታሪክ፣ የሴቶች አብላጫ የታየበት ያደርገዋል ብሏል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ባለፈው ቅዳሜ ቃለመሃላ ፈጽመው ስልጣን መያዛቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ታዋቂ የአገሪቱ ሴቶችን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት፣ በኢኮኖሚ ሚኒስትርነት፣ በፍትህ ሚኒስትርነት፣ በጤና ሚኒስትርነትና በሌሎች ወሳኝ ሃላፊነቶች ላይ መሾማቸውንም ዘገባው ጠቁሟል፡፡ ፡
ተሰናባቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ማሪያኖ ራጆይ ከሾሟቸው ሚኒስትሮች ውስጥ የሴቶቹ ድርሻ 36 በመቶ ብቻ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤አዲሱ መንግስት ለሴቶች ወሳኝ የስልጣን ቦታዎችን መስጠቱ በብዙዎች ዘንድ ተደናቂነት እንዳተረፈለትም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1246 times