Print this page
Saturday, 02 June 2018 12:05

የ“ደብተራው” አጭር ተውኔት 1ኛ ዓመት ይከበራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ግጥም በጃዝ የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ የ “ደብተራው” አጭር ተውኔት አንደኛ ዓመት ክብረ በዓልን ያከብራል፡፡
በዚህ ምሽት ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ከተላለፉት የ “ደብተራው” ተውኔቶች የተመረጡ ክፍሎች ተቀናብረው ለተመልካች የሚቀርብ ሲሆን፤ አንድ አዲስ የ “ደብተራው” ተውኔትም ይቀርባል ተብሏል፡፡ በተጨማሪም ገጣሚ በድሉ ዋቅጀራ (ዶ/ር)፣ በእውቀቱ ስዩም፣ አርቲስት ጌትነት እንየውና ሙአዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት የተመረጡ የጥበብ ስራዎቻቸውን ለታዳሚያኑ ያቀርባሉ፡፡
የመግቢያ ዋጋ 100 ብር ሲሆን ትኬቱ በጃፋር መፅሐፍት መደብር (ኮሜርስ ተወልደ ህንፃ) እንዲሁም ዮናስ መፅሐፍት መደብር (ብሔራዊ ትያትር በረንዳ) ይገኛል፡፡ በዕለቱም ራስ ሆቴል በሚገኘው፣ ጦቢያ ግጥምን በጃዝ ቢሮ ማግኘት እንደሚቻል አዘጋጆቹ ጠቁመዋል፡፡


Read 4022 times
Administrator

Latest from Administrator