አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር፤ በቶፊቅ ኑሪ ተደርሶ፣ በዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ የተዘጋጀውን “ከመጋረጃው በስተጀርባ” የተሰኘ ቴአትር የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ እንደሚያስመርቅ ገለጸ፡፡
ጭብጡን በአገር ጉዳይ ላይ ባደረገው በዚህ የሙሉ ሰዓት ቴአትር ላይ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን የሚሳተፉበት ሲሆን በምርቃቱ ላይ የባህልና ቱሪዝም ኃላፊዎች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚታደሙ ሀገር ፍቅር ቴአትር አስታውቋል፡፡