የወጣቱ ድምፃዊ ኢሳያስ ጂ (ኢሳ-ጂ) “አንኳኳ” አዲስ የሙዚቃ አልበም ለአድማጭ ቀረበ፡፡ በአገር፣ በፍቅርና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ 12 ዘፈኖችን የያዘው አልበሙ፤ ዜማና ግጥሙ በራሱ በድምፃዊው መሰራቱም ተገልጿል፡፡
ቅንብሩና ማስተሪንጉ ሙሉ በሙሉ በናትናኤል ተሾመ የተሰራ ሲሆን ራስ ጃኒ እና ናሽ የተሰኙ ድምፃዊያን በፊውቸሪንግ ተሳትፈውበታል ተብሏል። ጎጃም ሙዚቃ ቤት እያከፋፈለው እንደሚገኝም ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና