Monday, 21 May 2018 00:00

ባለፈው እትም ትዳርን ከመፍረስ ለማዳን ከሚረዱን ምክንያቶች አንዱን አስነብበናችሁዋል፡፡ የስነልብና ባለሙያዎች ትዳርን እንደአጀማመሩ ለማቆየት የሚረዱ በርካታ ጠቃሚ ነገሮችን የሚያማክሩ ሲሆን ለዚህ እትምም ለንባብ የተወሰኑትን መራርጠናል፡፡ አንድ መረጃ እንደሚጠቁመው በአሜሪካ 40-50% የሚሆኑ ትዳሮች የመፍረስ እድል ሲያጋ ጥማቸው በኢትዮጵያ ደግሞ በ30 አመት ውስጥ 45% ያህል ትዳር የመፍ

Written by 
Rate this item
(10 votes)


            በ14 ዓመቱ ታዳጊ ላይ የብልት መሰለብና የአካል ጉዳት ያደረሰበት ተጠርጣሪ አልተገኘም

          ታዳጊው ለከፍተኛ ህክምና ወደ ጳውሎስ ሆስፒታል ይመጣል
                 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን፣ ድባጤ ወረዳ፣ ዝግህ ቀበሌ፣ ልዩ ስሙ በካር ወንዝ በተባለ ቦታ ከብት በመጠበቅ ላይ የነበረው የ14 ዓመት ታዳጊ አበጠር ወርቁን ብልት በመስለብ ጥቃት ያደረሰበት ተጠርጣሪ እየተፈለገ ነው። የድባጤ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ንጋቱ ኢተፋ፤ ጉዳዩ ገና በምርመራ ላይ መሆኑንና ሰባት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
ባለፈው ሰኞ ግንቦት 6 ቀን 2010 ዓ.ም በግምት ከቀኑ ከ7፡00 እስከ 8፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ በካር በተሰኘው አካባቢ ታዳጊው ከብት ሲጠብቅ በነበረበት ወቅት አንድ ጫት በመቃም ላይ የነበረ ሰው አጠገቡ ሆኖ ለረዥም ሰዓት ሲያጫውተው እንደቆየና በድንገት ማጅራቱን ከመታው በኋላ ወድቆ ራሱን መሳቱን እንደነገራቸው የታዳጊው አጎት አቶ አያሌው አበረ ገልፀዋል፡፡ በአካባቢው ልማድ መሰረት የሰፈሩ ከብቶች የሚጠበቁት በተራ እንደሆነ የጠቆሙት የተጎጂው አጎት፤ በዕለቱም የከብት ጥበቃ ተራው የታዳጊው አባት እንደነበረና አበጠርም የአካባቢውን ከብቶች በመጠበቅ ላይ እንዳለ ጥቃቱ እንደደረሰበት ተናግረዋል፡፡
የፓዌ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ግርማ በየነ በታዳጊው ላይ ስለደረሰው የጉዳት መጠን ጠይቀናቸው ሲመልሱ፤ ህፃኑ ወደ ሆስፒታሉ ሲመጣ ብልቱ ተቆርጦ ፊቱ በከፍተኛ ሁኔታ ተጎድቶና የመንጋጋ ስብራት ደርሶበት እንደነበር አስታውሰው፤ ለሶስት ቀናት በሆስፒታሉ ህክምና ቢደረግለትም በሆስፒታሉ ያለው ራጅ ብቻ በመሆኑና በሲቲ ስካን የጭንቅላቱ ሁኔታ መታዬት ስለነበረበት ወደ አንጎሉ ደም እንዳይፈስ በመስጋት ባህርዳር ወደሚገኘው ፈለገ ህይወት ሆስፒታል ሪፈር ተፅፎለት ለተሻለ ህክምና እንደሄደ ነግረውናል፡፡ የጉዳቱን መጠን በተመለከተም “ብልት ተቆርጦ ሲሄድ አንድ አካልን ማጣት ከባድ ጉዳት ነው፤ ፊቱም ላይ የደረሰው አደጋ ቀላል አይደለም” ያሉት ሜዲካል ዳይሬክተሩ፤ ሲቲ ስካን ተነስቶና ሙሉ ምርመራ ተደርጎ የሚገኘው ውጤት ነው በህክምና ሙያ በዋናነት የጉዳቱን መጠን የሚገልፀው ብለዋል፡፡ ታዳጊው በአሁኑ ሰዓት በባህር ዳር ፈለገ ህይወት ሆስፒታል ማህበራዊ አገልግሎት ዘርፍ በኩል አስፈላጊው ምርመራና ህክምና እየተደረገለት መሆኑን የልጁን ጉዳይ በቅርበት እየተከታተሉ የሚገኙት በባህር ዳር ዩኒርቨሲቲ ረ/ፕሮፌሰር ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ከፈለገ ህይወት ሆስፒታል ገልፀውልናል፡፡
የ14 ዓመቱ አበጠር ወርቁ ለእናቱ የመጀመሪያ ለአባቱ ሶስተኛ ልጅ እንደሆነ የገለፁት አጎቱ አቶ አያሌው አበረ፤ ምንም የማያውቅ ልጅ እንዲህ አይነት አሰቃቂ ጥቃት ሲደርስበት የወረዳው ፖሊስ የተወሰኑ ሰዎችን እያሰረ ከመፍታት ውጭ የተጠናከረ ምርመራ እያደረገና ትኩረት እየሰጠ አለመሆኑ እንዳሳዘናቸው ገልፀው ጉዳዩ በመንግስት ደረጃ ትኩረት አግኝቶ ህፃኑ ፍትህ እንዲያገኝና አጥፊዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን ብለዋል፡፡
በፈለገ ህይወት ሆስፒታል ለልጁ ህክምናና ክትትል እያደረጉ የሚገኙት በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የመጨረሻ አመት የቀዶ ህክምና ተማሪ ዶ/ር ሲሳይ ሙሉቀን በበኩላቸው፤ ህፃኑ የብልት መቆረጥ የጭንቅላትና የአይን ጉዳት እንዲሁም የጥርስ መውለቅና ተደራራቢ ጉዳቶች የደረሰበትና በስለት ፊቱ የተቆረጠ በመሆኑ የጉዳቱ መጠን ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው፣ በአፉና በአንገቱ አካባቢ ኢንፌክሽን የተፈጠረ በመሆኑ የአንቲ ባዮቲክ ህክምና እየተደረገለት ነው ብለዋል፡፡ ዶ/ር ሲሳይ አክለውም፤ ልጁ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየነቃ መሄዱን፣ በአተነፋፈሱ በኩል ትንሽ ችግር ስለገጠመው በኦክስጅን ታግዞ እየተነፈሰ መሆኑን ጠቁመው፤ ብልቱ ላይ ካቲተር ተገጥሞለት ህክምናው ቀጥሏል ብለዋል፡፡
ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ የታዳጊውን ሙሉ ወጪ ሸፍነው ለማሳከም ቃል የገቡ ሲሆን የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን ህፃኑ ጳውሎስ ሆስፒታል መጥቶ እንዲታከምና ወጪውን ሚኒስቴሩ እንደሚሸፍን መግለፃቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 3422 times