Print this page
Monday, 07 May 2018 09:53

“ኃይሌ ፊዳ እና የግሌ ትዝታ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

  በዶ/ር አማረ ተግባሩ የተፃፈው “ኃይሌ ፊዳና የግሌ ትዝታ” የተሰኘ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሐፉ በ1960ዎቹ መጨረሻ በዋናነት በአውሮፓ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ እንዲሁም የመኢሶን መሪ በነበረው ኃይሌ ፊዳ ህይወት፤ ፖለቲካዊ ሚና እንዲሁም አጠቃላይ አብዮታዊ እንቅስቃሴ የሚያስቃኝ ነው ተብሏል፡፡
ስለ ኃይሌ ፊዳ ጨዋነት፣ አስተዋይነት፣ አርቆ አሳቢነትና ረቂቅነት የሚያወሳው መፅሐፉ፤ ለዛውን፣ ልዩ ፍቅሩንና ሥጦታውንም በተባ ብዕርና ባማረ ቋንቋ ይገልጽልናል ተብሏል፡፡ “የድህረ ዘውድ ኢትዮጵያ የሁሉንም ዜጋ ነፃነትና እኩልነት የሚያረጋግጥ፤ የደሀውንና የተበደለውን ወገን ዕድልና ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥ አቅጣጫ ከቀየሱት ወጣቶች ግንባር ቀደም የሆነው ኃይሌ ፊዳ ነውና ይህን መልካም ማስታወሻ ስላበረከተልን የዶ/ር አማረ ተግባሩ ባለውለታ ነን …” ብለዋል ፕሮፌሰር እንድሪያስ እሸቴ በመፅሐፉ ጀርባ ባሰፈሩት አስተያየት፡፡ በ236 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ በ111 ብር ከ50 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡  

Read 2538 times
Administrator

Latest from Administrator