Print this page
Monday, 07 May 2018 09:39

በታንዛኒያ ፈቃድ የሌላቸው ጦማሪያን 2 ሺህ ዶላርና የ1 አመት እስር ይቀጣሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የታንዛኒያ መንግስት 900 ዶላር በመክፈል የጡመራ ፈቃድ ሳያወጡ ሲሰሩ ያገኛቸውን ጦማሪዎች፤ የ2 ሺህ 200 ዶላር እና የ1 አመት እስር ቅጣት እንደሚያስተላልፍባቸው ከሰሞኑ ማስታወቁን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ባለፈው መጋቢት ወር በስራ ላይ ባዋለው አዲስ የድረገጽ ይዘት መመሪያ መሰረት፣ ተመዝግበው ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ያላገኙ ጦማሪዎች፤ ከዛሬ ጀምሮ በህገወጥ መንገድ ሲሰሩ ከተገኙ የተጠቀሰው እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ማስጠንቀቁን ዘገባው ገልጧል፡፡
ጦማሪያኑ አብረዋቸው የሚሰሩ ባለአክስዮኖችን፣ ካፒታላቸውን፣ ዜግነታቸውን፣ የሙያ ብቃታቸውን፣ የታክስ የምስክር ወረቀታቸውንና የመሳሰሉትን መረጃዎች ለሚመለከተው አካል እንዲያስመዘግቡና 900 ዶላር ከፍለው ፈቃድ ማግኘት እንዳለባቸው የሚያስገድደው መመሪያው፤ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን የሚጥስ፣ ኢ-ፍትሃዊ እርምጃ በሚል በአገሪቱ ጦማርያንና አክቲቪስቶች መተቸቱንም ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 1416 times
Administrator

Latest from Administrator