Sunday, 29 April 2018 00:00

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ምሁራን የመፍትሔ ሐሳብ እንዲያፈላልጉ ጥሪ አቀረቡ

Written by 
Rate this item
(10 votes)

 “ሃገር ለዋጭ ሐሳቦች ከምሁራኑ ሊፈልቁ ይገባል”

    ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ የመጣውን ጎሠኝነትና ብሔርተኝነት ከሃገራዊ ማንነት ጋር ማስታረቅ የሚቻልበትን የመፍትሄ ሐሳብ እንዲያፈላልጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ለምሁራን ጥሪ አቀረቡ፡፡ የአገሪቱ ፖለቲካዊ ችግሮች የተወሳሰቡ በመሆናቸው ችግሮቹን አገናዝቦ መውጫ መንገድ የሚያሳይ ምሁር ያስፈልገናል፤ ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፈው ሳምንት የባሕር ዳር ቆይታቸው፤ በዐውደ ጥናት ላይ የነበሩ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህራንን ያነጋገሩ ሲሆን፤ ምሁራኑ ለሀገሪቱ ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሄ የሚሆኑ የምርምር ሥራዎችን እንዲያቀርቡ ጠይቀዋል፡፡ አገር ለዋጭ ሐሳቦች ከምሁራኑ ይፈልጋሉ ሲሉም ተናግረዋል፡፡
ምሁራኑ በሀገሪቱ እየተስፋፋ ስለመጣው የብሔርተኝነት ጉዳይ ጥናት እንዲያደርጉ ያሳሰቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “መንግሥት ከምሁራኑ ጋር እስካልተመካከረ ድረስ ከገባንበት ችግር ልንወጣ አንችልም፤” ብለዋል፡፡ የብሔር ማንነትና ኢትዮጵያዊ ማንነት የሚታረቁባቸው የመፍትሔ ሐሳቦች ከምሁራኑ እንዲፈልቅም ጠይቀዋል፡፡

Read 7129 times