Tuesday, 20 March 2018 11:26

“ግጥም በጃዝ” ከውጭ ገጣሚያን ጋር በጥምረት የጥበብ ምሽት ይካሂዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ባለፈው ረቡዕ ለ80ኛ ጊዜ የግጥም ምሽቱን በድምቀት ያካሄደው “ጦቢያ ግጥም በጃዝ” የዛሬ ሳምንት ቅዳሜ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ከመጡ የውጭ ገጣሚያንና የኪነ-ጥበብ ሰዎች ጋር ልዩ የግጥም በጃዝ ዝግጅቱን ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በራስ ሆቴል አዳራሽ በጥምረት ያካሄዳል፡፡
በምሽቱ ከአሜሪካ፣ ከዴንማርክ፣ ከደቡብ አፍሪካና ከጀርመን የሚመጡ እውቅ ገጣሚያን ሥራቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ ፍሬዘር አድማሱ፣ ምህረት ከበደ፣ ረድኤት ተረፈ፣ ጆርጋ መስፍን፣ ምስራቅ ተረፈ እና ጣሰው ወንድም ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡


Read 5191 times