Tuesday, 13 March 2018 13:18

እንግሊዝ በናይጀሪያ እስር ቤት ለመክፈት 700 ሺህ ፓውንድ መድባለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

እንግሊዝ ናይጀሪያውያን እስረኞችን ወደ አገራቸው ልካ የእስር ጊዜያቸውን እንዲጨርሱ ለማድረግ፣በአገሪቱ ግዙፍ ወህኒ ቤት የምታስገነባበት 700 ሺህ ፓውንድ ያህል በጀት መያዟን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ እንግሊዝ ኪሪኪሪ በሚባለውና በሌጎስ የሚገኘውን የናይጀሪያ ትልቁን ወህኒ ቤት ለማስፋፋት ማቀዷን የጠቆመው ዘገባው፤ ሁለቱ አገራት ከ4 አመታት በፊት በፈጸሙት እስረኞችን አሳልፎ የመስጠት ስምምነት መሰረት እስረኞች ወደ አገራቸው ገብተው እንዲታሰሩ የማድረግ ሃሳብ መያዙንም አመልክቷል፡፡
በ2016 የፈረንጆች አመት ብቻ 320 ናይጀሪያውያን በተለያዩ የወንጀል ክሶች ቅጣት ተጥሎባቸው በእንግሊዝ በሚገኙ የተለያዩ እስር ቤቶች ውስጥ የእስር ጊዜያቸውን በማሳለፍ ላይ እንደነበሩ የጠቆመው ዘገባው፤ በእንግሊዝ ከሚገኙ የሌሎች አገራት እስረኞች ናይጀሪያውያን 3 በመቶውን እንደሚሸፍኑም አስታውሷል፡፡

Read 1568 times