Tuesday, 13 March 2018 12:53

ዎርልድ ሬሚት በቀላልና ርካሽ ዋጋ ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ እያስተላለፈ መሆኑን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ከግንባር ቀደም ዓለም አቀፍ ገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች አንዱ የሆነው ዎርልድ ሬሚት፣ ኒውዮርክ የሚገኙ 9 ሺህ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች በፈጣንና ዝቅተኛ ዋጋ ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ እንዲልኩ ማድረጉን አስታወቀ፡፡
ድርጅቱ ለዝግጅት ክፍላችን በላከው መግለጫ፣ ጊዜ ውድ በሆነበት የአሜሪካ (የውጭ አገር) ኑሮ፣ ደንበኞች ወደ አንድ ተቋም (ባንክ ወይም ገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች) በአካል መሄድ ሳይኖርባቸው በማንኛውም ቦታና ሰዓት፣ የድርጅቱን ድረ - ገፅ ወይም ሞባይል ስልካቸውን በመጠቀም ወደ ኢትዮጵያ ገንዘብ መላክ ይችላሉ ብሏል፡፡
ዎርልድ ሬሚት በኒውዮርክ ግዛት የሚኖሩትን ጨምሮ ከ50 በላይ በሚሆኑ አገራት የሚኖሩና የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ዜቶች የሚልኩትን ገንዘብ፣ እዚህ ያሉ ገንዘቡ የተላከላቸው ሰዎች በመላ አገሪቷ ከሚገኙ የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ቅርንጫፎች እንዲወስዱ ከባንኩ ጋር መዋዋሉን ገልጿል፡፡
የገንዘብ አስተላላፊው ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ኃላፊ ሻሮን ኪንያንጁይ፣ በዎርልድ ሬሚት በኩል ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ የገንዘብ ዝውውሮች ከፍተኛ ዕድገት እያሳዩ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፣ የኢትዮጵያ ዲያስፖራዎችም ሆኑ ተቀባዮቹ ከዎርልድ ሬሚት ጥራት ያለው አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ማረጋገጣችንን እንቀጥላለን፡፡ ኒውዩርክን ያካተተ አገልግሎት መጀመርና የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ወደ መረባችን መግባት ወደ ኢትዮጵያ ሃዋላ ለሚልኩ ሰዎች መልካም ዜና ነው ብለዋል፡፡
በወጣት ሶማሊያዊ ኢንተርፕረነር እስማኤል አህመድ እ.ኤ.አ በ2010 የተመሰረተው ዎርልድ ሬሚት ወደ ኢትዮጵያ ገንዘብ መላክ የጀመረው በተመሰረተ በዓመቱ በ2011 እንደሆነ የጠቀሰው መግለጫው፣ ኒውዮርክ በመጨመሩ አሜሪካ የዎርልድ ሬሚት ትልቁ የገንዘብ መላኪያ ገበያ እንደምትሆንና ኩባንያው በ2017 ከአሜሪካ የሚላከው ገንዘብ 200 ፐርሰንት ዕድገት ማሳቱን አመልክቷል፡፡ ዎርልድ ሬሚት ከFacebook, spotify, Netfliy እና Slack እንዲሁም ቀዳሚ ኢንቨስተሮች ከሆኑት Accel እና TCV 200 ሚሊዮን ዶላር ማግነቱን ገልጿል፡፡ ዋና መ/ቤቱ በለንደን ሲሆን የአሜሪካ ዋና መ/ቤት በዴንቨር፣ ክልላዊ ቢሮዎች ደግሞ በካናዳ፣ በደቡብ አፍሪካ፣ በፊሊፕንስ፣ በጃፓን፣ በአውስትራሊያና ኒውዝላንድ እንዳሉት መግለጫው አመልክቷል፡፡

Read 6459 times