የአፍሪካ አገራት ህገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ የነዳጅ ዝርፊያ፣ የአደንዛዥ እጽ ንግድና ኮንትሮባንድን በመሳሰሉ ተግባራት በሚፈጸሙ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውሮች በየዓመቱ በድምሩ 50 ቢሊዮን ዶላር ያህል እንደሚያጡ ተዘገበ፡፡
ተቀማጭነቱ በፓሪስ የሆነው አለማቀፉ የኢኮኖሚና የልማት ትብብር ተቋም ከሰሞኑ ያወጣውን ሪፖርት ጠቅሶ ሲኤንኤን እንደዘገበው፣ በምዕራብ አፍሪካ አገራት ከሚከናወነው ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር 80 በመቶውን የሚይዘው ከተፈጥሮ ሃብት በተለይ ደግሞ ከነዳጅ ዝርፊያ ጋር የሚያያዝ ነው፡፡
በአፍሪካ አገራት በህገ ወጥ መንገድ የሚዘዋወረው የገንዘብ መጠን ከፍተኛ መሆኑ የአገራቱን ልማት እንዳይፋጠን ከፍተኛ እንቅፋት መፍጠሩን የጠቆመው ዘገባው፤በአውሮፓ አገራትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር እጅግ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚንቀሳቀስ አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ