Print this page
Saturday, 24 February 2018 12:39

ማዶና “የማደጎ ልጄ ወደፊት የማላዊ መሪ ይሆናል” አለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አሜሪካዊቷ የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ ማዶና፣ ከማላዊ በማደጎ ወስዳ እያሳደገቺው የሚገኘው የ12 አመቱ ታዳጊ ዴቬድ ባንዳ፤ ወደፊት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት እንደሚሆን ያላትን ጽኑ እምነት መግለጧ ተዘግቧል፡፡
ከምታሳድጋቸው ስድስት የማደጎ ህጻናት መካከል አንዱ የሆነው ማላዊው ዴቪድ ባንዳ፣ እጅግ የሰላ አስተሳሰብና የአእምሮ ብቃት የተላበሰ ታዳጊ እንደሆነ ከሰሞኑ በትዊተር ድረገጽዋ ላይ በጻፈቺው ጽሁፍ የጠቆመቺው ማዶና፤ ለወደፊት እድሜው ሲገፋ አገሪቱን በብቃት የሚመራ ታላቅ ሰው እንደሚሆን በጽኑ አምናለሁ ማለቷን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ዴቪድ ባንዳን ጨምሮ ከማላዊ አራት ህጻናትን በማደጎ ወስዳ እያሳደገች እንደምትገኝ የጠቆመው የቢቢሲ ዘገባ፤ ከ12 አመታት በፊት ባቋቋመቺው ሬዚንግ ማላዊ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት አማካይነት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገች እንደምትገኝም አውስቷል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ከ5 አመታት በፊት ማዶና በአለም አደባባይ ለአገራችን የምታበረክተውን አስተዋጽኦ ከሚገባው በላይ አጋንና በመናገር ላይ ናት በሚል ወንጅሏት እንደነበርም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 1507 times
Administrator

Latest from Administrator