Monday, 05 February 2018 00:00

የሄለን በርሄ “እስኪ ልየው” የፊታችን አርብ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

  በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ኮንሰርት ታቀርባለች

    የድምፃዊት ሄለን በርሄ “እስኪ ልየው” የተሰኘ አልበሟና “ፊት አውራሪ” ለሚለው ዘፈኗ የተሰራው ቪዲዮ ክሊፕ የፊታችን አርብ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ፣ ወሎ ሰፈር በሚገኘው ማማስኪችን ይመረቃል፡፡
በምሽቱም ድምጻዊት ሄለን “ፊታውራሪ”ን ጨምሮ የተለያዩ ዘፈኖቿን የምታቀርብ ሲሆን ሌሎች ድምፃዊያንም እንደሚያቀነቅኑ ታውቋል፡፡ በሌላ በኩል የድምጻዊቷ ማናጀር አቶ በረከት ተሾመ እንደገለጹት፤ ድምጻዊቷ ከአብይ ፆም በኋላ በአዲስ አበባና በክልሎች ትልልቅ ኮንሰርቶችን የምታቀርብ ሲሆን በቀጣይም በውጭ አገራት ተመሳሳይ ኮንሰርቶች የማቅረብ እቅድ አላት፡፡  
በአንድ የዘፈን አልበሟ ተቀባይነት፣በአንድ የዘፈኗ ቪዲዮ ላይ አነጋጋሪ ስሆነው አልበሟና ስለተሰማራችበት የበጎ አድራጎት ድርጅት ከአዲስ አድማስ ለቀረበላት ጥያቄ በሰጠችው ምላሽ፣ አልበሟ ጥሩ ተቀባይነት ማግነቱን፣ በህፃናት ካንሰር ከUNDP ጋር በሴቶች ዙሪያ እንደምትሰራ የገለፀች ሲሆን አለባበሷ በቪዲዮው ዳይሬክተር ስንታሁ ሲሳይ ትዕዛዝ መለበሱን ገልፃ “በዚህ አለባበስ ህዝቡንም ሆነ ሚዲውን አስቀይሜ ከሆነ ይቅርታ እጠይቃለሁ” ብላለች፡፡

Read 5034 times