Saturday, 03 February 2018 13:12

“ትርታ” ተከታታይ ድራማ፣ ነገ በፋና ቴሌቪዥን ይጀምራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በክላስ አክት ፊልም ፕሮዳክሽን እየተሰራ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 1፡30 የሚቀርበው “ትርታ” የተሰኘ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ነገ ምሽት በፋና ቴሌቪዥን እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡  
የድራማው ደራሲ  ሶፎንያስ ታደሰ ሲሆን ዳይሬክተሩ ልዑል ተፈሪ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በድራማው ላይ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን የሚሳተፉበት ሲሆን ከነዚህም መካከል፡- ኤልሳቤጥ መላኩ፣ አላዛር ሳሙኤል፣ ጌታቸው ስለሺ፣ ዲበኩሉ ታፈሰ፣ እታፈራሁ መብራቱ፣ ዝናቡ ተስፋዬ፣ አበበ ባልቻ፣ ፍሬው አበበ፣ ናርዶስ እንግዳ፣ ያፌት ሄኖክ፣ ሜሮን እንግዳና ሌሎችም እንደሚተውኑበት አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡   
ወንጀል ነክ ልብ አንጠልጣይ ዘውግ ያለው ድራማው፤ በአራት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን በ1950ዎቹ ዓመታት በአንድ ዘመናዊ ነጋዴና በአንድ ኢትዮጵያዊ ወጣት ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ነው ተብሏል፡፡ ድራማው በታሪክም ሆነ በምስል ጥራቱ ደረጃውን የጠበቀ እንደሆነም አዘጋጆቹ ጠቁመዋል፡፡

Read 2546 times