Print this page
Tuesday, 30 January 2018 00:00

የአፍሪካ ህብረት ትራምፕን ሲያወግዝ፣ ሙሴቬኒ አድንቀዋቸዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)


               “ትራምፕ የልቡን ስለሚናገር እወደዋለሁ” - የኡጋንዳው መሪ ዮሪ ሙሴቬኒ

   የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ናህማት፣ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ በአፍሪካውያን ላይ አስጸያፊ ንግግር ማድረጋቸው አግባብነት የሌለውና የአገራቱ መሪዎች በጋራ የሚያወግዙት ነው ቢሉም፣ የኡጋንዳው መሪ ዮሪ ሙሴቬኒ በአንጻሩ፣”ትራምፕ ምን ይሉኝ ሳይል የልቡን ስለሚናገር እወደዋለሁ፤ አደንቀዋለሁ” በማለት በዘለፋው አለመቀየማቸውን ገልጸዋል፡፡
ትራምፕ በቅርቡ አፍሪካውያንንና ሃይቲያውያንን በሚመለከት አስጸያፊ ንግግር ማድረጋቸው በተመድ ሳይቀር መነቀፉን ያስታወሰው ኒውስ 24፤ የህብረቱ ሊቀመንበርም ከትናንት በስቲያ ከአዲስ አበባ በሰጡት መግለጫ፣ ዘለፋው አፍሪካውያንን ያስከፋና የጥላቻ ንግግር ነው፤ ህብረቱም አጥብቆ ያወግዘዋል ያሉ ሲሆን  ህብረቱ በማካሄድ ላይ ያለውን ጉባኤ ሲያጠናቅቅ በጉዳዩ ላይ ይፋዊ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል፡፡
የኡጋንዳው መሪ ዮሪ ሙሴቬኒ በበኩላቸው፣ ትራምፕ አፍሪካውያንን በተመለከተ ያለውን አመለካከትና ስሜት ሳይሸፋፍን እቅጩን ስለሚናገር እወደዋለሁ፤ እኛ አፍሪካውያን ያለብንን ድክመት ለመናገር ቃላት አይመርጥም፣ አካፋን አካፋ ይላል በማለት በትራምፕ ንግግር አለመቀየማቸውን ገልጸዋል ብሏል ዘገባው፡፡

Read 3051 times
Administrator

Latest from Administrator