በሳይቤሪያ በምትገኘው ኦይማይኮን የተባለች የገጠር መንደር ውስጥ በሳምንቱ መጀመሪያ ከዜሮ በታች ኔጌቴቭ 62 ዲግሪ ሴንትግሬድ የደረሰ ሃይለኛ ቅዝቃዜ የተመዘገበ ሲሆን ቅዝቃዜው በመንደሯ የነበረውን የሙቀት መለኪያ መሳሪያ በመስበር ከጥቅም ውጭ ማድረጉ ተነግሯል፡፡
እ.ኤ.አ በ1993 ከዜሮ በታች 67.7 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ሃይለኛ ቅዝቃዜ የተመዘገበባት መንደሯ፤500 ያህል ቋሚ ነዋሪዎች እንደሚገኙባትና ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ያላት መሆኗን የጠቆመው ዘገባው፣ ነዋሪዎች ቅዝቃዜውን ለመቋቋም ተቸግረው እንጨትና ከሰል በማቀጣጠል ህይወታቸውን ለማትረፍ ደፋ ቀና እያሉ እንደሚገኙ አመልክቷል፡፡
በአለማችን ታሪክ ዝቅተኛው የሙቀት መጠን ሆኖ የተመዘገበው በምስራቃዊ አንታርክቲካ እ.ኤ.አ በ2013 የተከሰተው ከዜሮ በታች ኔጋቲቭ 94.7 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ቅዝቃዜ እንደነበር ዘገባው አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ