Print this page
Saturday, 20 January 2018 12:57

ቻይናውያን በኮሌጅ ፈተና የመምህራቸውን ስም ተጠይቀዋል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   ሹዋን ቮኬሽናል ኮሌጅ  ኦፍ ካልቸር ኤንድ ኮሙኒኬሽን የተባለው የቻይና ኮሌጅ ተማሪዎች ሰሞኑን በወሰዱት የሴሚስቴር ማጠቃለያ ፈተና ላይ የመምህራቸውን ስም እንዲጽፉ የሚያዝዝ አንድ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል፡፡
ቤጂንግ ታይም እንደዘገበው፤ተማሪዎቹ የሰባት ሰዎችን ፎቶግራፍ የያዘ የጥያቄ ወረቀት የቀረበላቸው ሲሆን ከሰባቱ መካከል መምህራቸውን መርጠው ከስሩ ስሙን እንዲጽፉ ተጠይቀዋል። ጥያቄውን በትክክል የመለሱት ተጨማሪ ማርክ ባይሰጣቸውም፣ የተሳሳቱና መምህራቸውን ወይም ስሙን መለየት ያልቻሉት ግን ካገኙት ውጤት ላይ 41 ነጥቦች ተቀንሶባቸዋል፡፡
በኮሌጁ የሚያስተምሩት ሁ ቴንግ እንደሚሉት፤ በአይነቱ የመጀመሪያው የሆነውን ይህን ጥያቄ በፈተናው ውስጥ ማካተት ያስፈለገው፣ ተማሪዎች ከመደበኛ ትምህርታቸው ባሻገር በዙሪያቸው ላለው ነገር ምን ያህል ትኩረት እንደሚሰጡ ለመገምገም በሚል ነው፡፡ ይህ የኮሌጅ ፈተና ጥያቄ በቻይናውያን ማህበራዊ ድረገጾች መነጋገሪያ ጉዳይ ሆኖ መሰንበቱን የጠቆመው ዘገባው፣ አንዳንዶች ክፉኛ ቢያብጠለጥሉትም የተወሰኑት ግን የመምህርን ስም ማወቅ ግዴታ ነው ሲሉ ድጋፋቸውን እንደሰጡት አመልክቷል፡፡

Read 1463 times
Administrator

Latest from Administrator