Saturday, 20 January 2018 12:31

የእግዜር ስላቅ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ነገ እኩለ-ቀን ላይ
ምሳ አብረን ልንበላ ተቃጥረን ነበረ
ጓዴን ዛሬ ማታ
ከቀጠሮው በፊት ሞት ቀድሞት አደረ
ይህ ገብቶት ነው ለካ
እኛ ስንቃጠር እግዜር ከላይ ሆኖ ሲስቅ የነበረ፡፡

ፈሪሃ እግዚአብሔር
‹እግዚአብሔርን ፍራ› እያለ ሲሰብከኝ በነጋ በጠባ    እግዜርን ፈርቼ
እግዜርን ሸሽቼ
ደብር መሄድ አቆምኩ ገነት እንድገባ፡፡

መልክኣ ሰብእ
አውቃለሁ ኃጢአቴን ብዙ በድያለሁ
ቃልህን ገድፌ ሺ ጊዜ ስቻለሁ፤
ቢሆንም ቢሆንም
ንስሀ ለመግባት ስለማይሆንልኝ
አቤቱ ጌታ ሆይ ና ተሰቀልልኝ!
(“አገሬን ሰቀሏት” ከተሰኘው የገጣሚ
ደሱ ፍቅር የግጥም መድበል የተወሰደ)

Read 1435 times