Saturday, 06 January 2018 12:02

አየር መንገድ አዲስ የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

ደንበኞች ባሉበት ሆነው የአየር መንገዱን ሙሉ አገልግሎት ማግኘት ያስችላቸዋል

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞቹ ባሉበት ቦታ ሆነው የአየር መንገዱን የተለያዩ አገልግሎቶችን ማግኘት የሚችሉበትን የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ (አፕሊኬሽን) ተግባራዊ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
ይህ የመረጃ መተግበሪያ (አፕሊኬሽን) ደንበኞች ተንቀሳቃሽ ስልካቸውን በመጠቀም የበረራ ቲኬት መቁረጥ፣ ክፍያ መፈፀምና የበረራ ወንበር ቁጥር ባሉበት ቦታ ሆነው ለመምረጥ የሚያስችላቸው ነው ተብሏል፡፡
የገንዘብ ክፍያም በሞባይል ባንኪንግ አሊያም በኢንተርኔት መፈፀም ይቻላል ተብሏል። መተግበሪያው በጎግል ፕሌይ እና በአፕስቶር እንደሚገኝና ማንኛውም ሰው ዳውንሎድ አድርጎ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችል አየር መንገዱ ለሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫው አስታውቋል፡፡
ደንበኞች ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ በእንግሊዝኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ ጀርመንኛ፣ አረብኛና ሌሎች የውጭ ሃገር ቋንቋዎች አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ታውቋል፡፡ ይህ መተግበሪያ በአየር መንገዱ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያዎች መሰራቱ የተገለፀ ሲሆን አገልግሎቱ ለደንበኞች ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችል የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ገልፀዋል፡፡

Read 4032 times