በቀዳማዊ ቴዎፍሎስ ፓትሪያርክ ህይወትና መንፈሳዊ አገልግሎት ዙሪያ በሚያጠነጥነው መፅሀፍ ላይ ዛሬ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ሆቴል ዳሰሳና ጥናታዊ ፅሁፍ እንደሚቀርብ የፕሮግራሙ አዘጋጆች ገለፁ፡፡
“የፓትሪያርክ ቴዎፍሎስ አሻራዎች” በሚል ርዕስ በሚካሄደው በዚህ ፕሮግራም ላይ አቡነ ማቴዎስ (ዶ/ር)፡- የፓትሪያርክ ቴዎፍሎስ አሻራ ከትምህርት አንፃር፣ ዶ/ር አግደው ገዴ፡- የፓትሪያርኩ አሻራ ከልማት አኳያ፣ ዶ/ር ምክረስላሴ ገ/አማኑኤል፡- ከውጭ ግንኙነታቸውና ከታሪክ አንፃር፣ መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ከቤተክርስቲን አደረጃጀት ፅንሰ ሀሳብ አንፃርና ዶ/ር አሰፋ ዘሩ፡- በአጠቃላይ በመፅሀፉ ላይ ዳሰሳ እንደሚያቀርቡ የፕሮግራሙ አዘጋጆች ጠቁመዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ ፓትሪያርኩ አቡነ ማቲያስንጨምሮ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶ/ር ሂሩት ወ/ማሪያም፣ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር፣ የወመዘክር ሀላፊዎችና የተለያዩ የሀይማኖት አባቶች እንደሚገኙም ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና