Monday, 18 December 2017 13:37

የ2018 የ”ጎልደን ግሎብ” ሽልማት ዕጩዎች ታወቁ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ለ75ኛ ጊዜ ለሚከናወነው የ2018 “ጎልደን ግሎብ” ሽልማት በዕጩነት የቀረቡ ፊልሞች ዝርዝር ባለፈው ሰኞ ይፋ የተደረገ ሲሆን  ዘ ሼፕ ኦፍ ዎተር የተሰኘው ፊልም፣ ምርጥ ዳይሬክተርና ምርጥ ሴት ዋና ተዋናይትን ጨምሮ በሰባት ዘርፎች ለሽልማት በመታጨት ቀዳሚነቱን ይዟል፡፡
ስሪ ቢልቦርድስ እና ዘ ፖስት የተሰኙት ፊልሞችም እያንዳንዳቸው በስድስት ዘርፎች ለሽልማት የታጩ ፊልሞች እንደሆኑ የዘገበው ቢቢሲ፤ ሌዲ በርድ የተሰኘው ፊልም በበኩሉ፣ በአራት ዘርፎች በመታጨት ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን አመልክቷል፡፡
በቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማዎች ዘርፍ፣ ለዘንድሮው የ”ጎልደን ግሎብ” ሽልማት ከታጩት መካከል፣ በስድስት የተለያዩ ዘርፎች የታጨው ቢግ ሊትል ላይስ በብዛት በመታጨት ቀዳሚነቱን ይዟል ተብሏል፡፡
የሆሊውድ የውጭ ፕሬስ ማህበር የሚያዘጋጀው አመታዊው የ”ጎልደን ግሎብ” ሽልማት አሰጣጥ ስነስርዓት በመጪው ጥር ወር መጀመሪያ ላይ በቢቨርሊ ሂልስ ካሊፎርኒያ በደማቅ ሁኔታ ይከናወናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read 1242 times