Monday, 18 December 2017 13:33

በአዕምሮ ህመም ላይ ያተኮረ ነጠላ ዜማ ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከብሬማን ፊልም ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር በአዕምሮ ህመም ላይ ያተኮረና ለማህበሩ ግንዛቤ ያስጨብጣል የተባለ ነጠላ ዜማ ከነገ በስቲያ ሰኞ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይመረቃል፡፡
የአገራችን እውቅ አቀንቃኞችና የሙዚቃ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል የተባለው ነጠላ ዜማ፣ ቪዲዮ የተሰራለት ሲሆን የምርቃት ስነ-ስርዓቱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የሙዚቃ ሰዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎችና የህክምና ባለሙያዎች በተገኙበት እንደሚካሄድ ሆስፒታሉ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

Read 1422 times