አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከብሬማን ፊልም ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር በአዕምሮ ህመም ላይ ያተኮረና ለማህበሩ ግንዛቤ ያስጨብጣል የተባለ ነጠላ ዜማ ከነገ በስቲያ ሰኞ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይመረቃል፡፡
የአገራችን እውቅ አቀንቃኞችና የሙዚቃ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል የተባለው ነጠላ ዜማ፣ ቪዲዮ የተሰራለት ሲሆን የምርቃት ስነ-ስርዓቱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የሙዚቃ ሰዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎችና የህክምና ባለሙያዎች በተገኙበት እንደሚካሄድ ሆስፒታሉ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና