Monday, 18 December 2017 12:35

ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዎችን ያስመርቃል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው የሊንከን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቢዝነስ አድምኒስትሬሽን በሁለተኛና በመጀመሪያ ዲግሪ ያስተማራቸውን ተማሪዎች  ለሁለተኛ ጊዜ ያስመርቃል፡፡
ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ፣ ይህን የትምህርት መርሃ ግብር በተለይ የንግድ ስራ አመራር ላይ አተኩሮ የሚሰጥ ሲሆን ለ7ኛ ጊዜ በMBA እና ለ2ኛ ጊዜ በBA ፕሮግራም ያስተማራቸውን ተማሪዎች ነው ነገ በአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን የስብሰባ ማዕከል የሚያስመርቀው፡፡
በምርቃት ስነ ስርአቱ ላይም የፐብሊክ ፋይናንስ ኢንተርፕራይዝ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ጀነራል ዶ/ር ስንታየሁ ወ/ሚካኤል፣ የሊንከን ዩኒቨርሰቲ ካሊፎርኒያ ፕሮፌሰርና የዩኒቨርሲቲው የባላደራ ቦርድ ሊቀ መንበር ዶ/ር አላን ሳምሶን እና የአሜሪካ ኤምባሲ ተወካይ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የመንግስት ባለስልጣናት ይገኛሉ ተብሏል፡፡

Read 2980 times