Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 14 April 2012 13:04

የህፃናት ጥግ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ውድ እግዚአብሔር፡-

በድሮ ጊዜ ብዙ ተዓምራት ሰርተሃል፡፡ አሁን ለምን መስራት ተውክ?

-ፌቨን-

ውድ እግዚአብሔር፡-

ለእረፍት በወጣን ጊዜ ዝናብ ሲዘንብ ስለነበረ አባቴ አብዶ ነበር፡፡ ሰዎች ስላንተ ማለት የማይገባቸውን ነገር ሁሉ ሲልህ ሰምቻለሁ፡፡ ሆኖም ግን እንደማትጐዳው ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

(ወዳጅህ ነኝ - ማንነቴን ግን እንዳትጠይቀኝ)

ውድ እግዚአብሔር፡-

የተሻለ እግዚአብሔር ለመሆን የሚችል ማንም ያለ አይመስለኝም፡፡ እንዲህ የምለው ደግሞ አሁን አንተ እግዚአብሔር ስለሆንክ እንዳልሆነ እንድታውቅ እፈልጋለሁ፡፡

-ቻርልስ-

ውድ እግዚአብሔር፡-

ቃየል እና አቤል የየራሳቸው ክፍል ቢኖራቸው ኖሮ እርስ በርስ አይጋደሉም ነበር፡፡ ለእኔና ለወንድሜ ለላሬ ይሄ ነገር ሰርቶልናል፡፡

-ዴቭ-

ውድ እግዚአብሔር፡-

እግዚአብሔር መሆንህን እንዴት አወቅህ?

-ሳሚ-

ውድ እግዚአብሔር፡-

እባክህ የፈረስ ግልገል ላክልኝ፡፡ ከዚህ ቀደም ምንም ነገር ጠይቄህ አላውቅም፡፡ መዝገብህን መመልከት ትችላለህ፡፡

-ጆሴፍ-

ውድ እግዚአብሔር፡-

እባክህ ሚኪን ወደ ሌላ ሰፈር ውሰደው፡፡ እባክህ … እባክህ!!

-ኤርሚ-

ውድ እግዚአብሔር፡-

አንተ እንዴት ልትፈጠር ቻልክ?

-ሳራ-

ውድ እግዚአብሔር፡-

እኔ ጥሩ ወይም መጥፎ ስሆን ታውቃለህ እንዴ? ወይስ የገና አባት ብቻ ናቸው የሚያውቁት?

-ሮዚ-

 

 

Read 2695 times Last modified on Saturday, 14 April 2012 13:07