Sunday, 03 December 2017 00:00

ደቡብ ኮርያ ለ1.6 ሚሊዮን ዜጎቿ የዕዳ ስረዛ ልታደርግ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የደቡብ ኮርያ መንግስት አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች የገንዘብ ጫና ለማቃለል በሚል 1.6 ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎቹ የነበረባቸውን የገንዘብ ዕዳ በከፊል ለመሰረዝ ማቀዱን ቢቢሲ ከትናንት በስቲያ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት የዕዳ ስረዛውን ተግባራዊ የሚያደርገው እስከ 9ሺህ 128 ዶላር ዕዳ ላለባቸውና የመክፈል አቅም ለሌላቸው ዜጎቹ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ ስረዛው የሚመለከታቸው ዜጎች ከመጪው የካቲት ወር ጀምሮ የዕዳ ስረዛ እንዲደረግላቸው ማመልከቻ እንዲያስገቡ ጥሪ ማቅረቡን አመልክቷል፡፡ ለዕዳ ስረዛው ማመልከት የሚችሉት ዜጎች ወርሃዊ ገቢያቸው ከ910 ዶላር በታች የሆነና ዕዳቸውን ለመክፈል ከአስር አመታት በላይ የተሰቃዩና ያልተሳካለቸው መሆናቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ ብቻ እንደሆኑም ዘገባው ገልጧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት “የደስታ እርዳታ” በሚል የሰየመውና ዕዳቸውን ለመክፈል ያልቻሉ ችግረኛ ደቡብ ኮርያውያንን አቅም የማጎልበት አላማ ያለው ፕሮግራሙ፤ ከዜጎች ያገኝ የነበረውን ገንዘብ ከሌሎች አበዳሪዎች አግኝቶ ለማካካስ ማቀዱንም ዘገባው አስረድቷል፡፡

Read 1776 times