በሩስያ ሳይንስ እና ባህል ማእከል በሚደረግ ሳምንታዊ የፊልም ውይይት “ዘመናዊ የፊልም ንቅናቄ” ለውይይት እንደሚቀርብ አላቲኖስ የፊልም ሰሪዎች ማህበር አስታወቀ፡፡ በመጪው ሳምንት ሐሙስ ከቀኑ 11 ሰዓት የሚደረገውን ውይይት በርእሱ የዩኒቨርሲቲ መመረቂያ ፅሑፉን እያዘጋጀ ያለው የፊልም ባለሙያ ምኒሊክ መርእድ እንደሚመራው ማወቅ ተችሏል፡፡ በውይይቱ ከዓለም የሲኒማ ቴክኒክ አንፃር የሩስያዊው ሰርጌይ ኢዘንስታይን እስከ ኢትዮጵያዊው ሚሼል ፓፓቲኪስ ሥራዎች ውይይት ይደረግባቸዋል፡፡