Print this page
Saturday, 25 November 2017 09:14

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፤ አጠቃላይ ሀብቱ 21 ቢ. ብር መድረሱን ገለፀ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አጠቃላይ የሃብት መጠኑ 21 ቢሊዮን ብር መድረሱን የገለፀ ሲሆን በተለያዩ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ለተሰማሩ ባለሀብቶች የሰጠው የብድር መጠንም 10.9 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ አስታውቋል፡፡
የባንኩ የባለአክሲዮኖች 18ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ህዳር 9 ቀን 2010 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ባከናወነበት ወቅት በቀረበው ሪፖርት ላይ
እንደተጠቀሰው፤ በበጀት ዓመቱ ከታክስ በፊት  681.5 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡ ተጠቅሷል፡፡
አመታዊ ትርፉም ካለፈው አመት አንፃር የ48.6 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየ የጠቆመው ባንኩ፤ ባለፈው ዓመት 50 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በአዲስ አበባና ክልል ከተሞች መክፈቱንም አስታውቋል፡፡ በአጠቃላይም የቅርንጫፎቹን ብዛት 180 ማድረሱንና 73 አዳዲስ የካርድ ገንዘብ ከፋይ ማሽኖችን (ATM) በተለያዩ ሆቴሎችና ቅርንጫፎች መትከሉን አመልክቷል፡፡ ባንኩ አገልግሎቶቹን በራሱ ህንፃ ላይ ለማከናወን የግዥና የግንባታ ስራዎች እየሰራ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን በጉባኤው ላይም ለቀጣይ ሶስት ዓመታት ባንኩን በበላይነት የሚመሩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት መምረጡን አስታውቋል፡፡

Read 3226 times
Administrator

Latest from Administrator