Tuesday, 21 November 2017 00:00

ማስታወሻ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 የ‹‹ዘበት እልፊቱ››ን የሰለሞን ደሬሳን እልፊት ለመዘከር፤ አላፊው ራሱ “The Tree” በሚል ርዕስ፤ እንደ ወርቅ አንጥሮ - እንደ ጨርቅ ጠቅልሎ በእንግሊዝኛ የነደፈውን እውነት እና ውበት፤ በላይ ግደይ እንዲህ ወደ አማርኛ ተረጎመው፡፡ እኔ የተርጓሚው ወዳጅ አነበብኩት፣ ወደድኩት እናንተም እንድታዩት ለአዲስ አድማስ ላኩት፡፡
ዛፉ

ፍሬ ዘር ይኖር ኣለ       
እንዳቅሚቲ ለዘላለም፡ ክንብንቤ ወድቆ፡    
‘ተወለደ፡ ሞተ’ ምን ቢኾንም፡ ልደት ናፍቆ፤                             
ቱክ… ቱክ…ቱክ… ለዅልኽም፡ ለያንዳንድኽ፡        
ቱክ…ቱክ… እንዳለች ናት፡
ቱክ… ቱክ… ባይዋ ሰዓት፤       
‘ያው እንደኔው፡ እኔን ሰምታ፡’ ድልልዋም ልብ፡ ልቢት ከንቱ፡               
ጊዜ ላይ ትልታዩን፡ የጊዜን ቍርጭራጭ፡ የጊዜን ኰረቱ ----  

ዱሮ ቀንበጥ! እዩትልኝማ፡     
ይሣሡለት ለጋ፡ ያባባ ድንቅዬ፡                   
እንዳይኗ የማሙዬ                                              
ስታይ እምነት ጥላ፤                                                       
ጕጉ፡ ድንግል እንዳራስ ናላ፤          
ዕሺ፡ ዕሰየው ለየቱም ትንፋሽ፤       
ተራቢ የርጥብ ዓፈር፡ የርጥብ መሬት፡
ተጠሚ የማይ ሕይወት፡
ሙላው ሥራሥሩ
ለምለም ከንፈር የማሙዬ፡        
ለወትሮው ስትደቀን        
ኣነፍንፋ ከጡት ጠረን----

ይኸው ደሞ ያቅል ጌታ ኣድጎ፡ ተመንድጎ!    
ከቆመበት ጸንቶ ሺ ዓመት እሱ
ይኸው ይኖር ዛፍ ለጋሱ።
ኣድባር፡ ኣውጋር ኣምኖ ኣበባዉን ይገልጥ፡                 
ጫፉ፡ ቅርንጫፉ ሙሉ ዓቅሙን ይለጠጥ፡-  
ድባብ የላይ
ለዘረ ወፍ ለተንጫጪ፡              
ለፍንድቅ ልጅ ለቦራቂ:           
ለጦጣ ዥውዥው ባይ፤
ለወፊቷ ጎጆ ወጪ፡         
ለርጅናው ለጥላ ሻይ፤                                         
ለሩቅ ኺያጅም ቢራቢሮ።   
ለኒኽ ኹላ በላይ ኑሮ
ዃላ ሊንቀለቀል አለለከት      
በራሱ፡ በደረቀ፡ በገዛው ሞት።

ዛፉ፡ ዛፉ!
ትዕግሥት ኣያልቅበት ዲበ መምህር፤
ዘፈንዋ ስለ ፍቅር                   
ለሰማዩ ውዷ ከታች ምድር።
ለሕማሙ፡ ለ(ዕ)ጹቡ ድንቅ፡ እማኝ፤
መካያው ላይ ክንዶቹም የዛፉ
ዓሳረኛው ሥጋን ያሳረፉ።  

የትልቁ ሠሪ ቢጋር ውቅር፡                    
ኣጐበር  ለኪዳኑ፤ ኣበውም ጐምቱው ከሥር፤            
ዓዛኝ ኣጋር ለደጋግ ተመስጦ፡ ለንቃቱ፤  
  ዛፉ፡ ኣዎን፡ የሰጠኝ የሰጠዅ
  ለበኽሯ ፍቅሬ ያበባ በረከት ከበኵራቱ።     

ዝም ዕክሙ ልባይምሮ ሥሩ ጠሊቅ  
ከለፍላፊት ራሴ ይልቅ፤
ማርያም ማርያም ካሉባቱ፡ ከቦታዪት ጭገሬታ- -
የሚሰማኽ ዘመድ፡ የሚያምኽ ቋሚ ወዳጅ፡
ስማኝና ብቅ በል፡ ብቀል ካላውቀው መቃብሬ፤
ሥሥ ኣሥራውኽ ይዝለቁና ወደ መለያያ
ያጥንቶቼ፡       
ዋጠኝ ባቅልኽ፡ በትዕግሥቶች፡
ዋጠኝ ወደጦፉት፡ ወዳንድነት የፍቅረኞች።

ታዲያ፡ ታዲያ፡ ከቶ ኣይጠፋኝ ደጉ ዕውቀት፤         
እኔ’ንጂ መች ኣንተ ትፈራና የነበልባል ብናኝ
ዕርገት።        
ኣዎ፡ ዓውቃለዅ፡
ስትኼድ እኔም የለዅ፤
ኣንተም ብትኾን የለኽ፡ ኣልቀኽ።  

Read 1649 times