Monday, 13 November 2017 10:43

ልጅነት

Written by 
Rate this item
(27 votes)

  የንጋት ጮራ
ዓይኔ ላይ አበራ
ጮ¤ ፎከረ አቅራራ
ልቤ እንዳይደነግጥ
እንዳልሸበር እንዳልፈራ፡
የምሽት ዳፍንት
የሽምግልና ጥፊ
ወንድ አንጀት አለስላሽ
ልጅነት ቀጣፊ
እንደቱታ ራስ ሚመታ
ሳይቀጥፈኝ በሽታ
የንጋት ጮራ እንዳይጠፋ
ወኔዬ እንዳታንቀላፋ
ጩህ ሸልል አቅራራ
ልጅነቴ አደራ
እንዳልሸበር እንዳልፈራ
(ልጅነት፣ ሰለሞን ደሬሳ፣ 1963 ዓ.ም)

ጋሽ አስፋው ዳምጤ፣ ስለ ሰሎሞን ደሬሳ…
 “…ሰሎሞን አንባቢ ነበረ፡፡ በጣም በጣም በጣም አንባቢ!... ቮረሺየስ አንባቢ!... ለትምህርቱ ግድ የለውም፡፡ በኋላ ላይ ሳስበው፣ ሰሎሞን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁን ማደሪያውና መኖሪያው እንጂ፣ መማሪያው አላደረገውም ነበር - ቁርስና ምሳ እየበላ ማደር፡፡ ትምህርቱን አይፈልገውም ነበር፡፡ እሱ ራሱን ነው የሚያስተምረው፡፡ ቤተ-መጻህፍት ሄዶ የሚያነብበው ሌላ ነገር ነበር እንጂ፣ ለክፍል ፈተናው አልነበረም…”
(ደራሲና ሃያሲ አስፋው ዳምጤ፣ ከጥቂት ወራት በፊት በአዲስ አድማስ  ጋዜጣ፣ ከጋዜጠኛ ሰሎሞን አበበ ቸኮል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ስለ ገጣሚ ሰሎሞን ደሬሳ ከተናገሩት የተወሰደ)

Read 8507 times