የሩሲያ ፌዴሬሽን ኤምባሲ ብሄራዊ የአንድነት ቀንን በማስመልከት የአዲስ አበባን እና የሳንት - ፔተርስቡርግን እህትማማች ከተማነት ምክንያት በማድረግ ዛሬ ከቀኑ 8፡45 ጀምሮ በሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል (ፑሽኪን አዳራሽ) ከሩሲያ የመጡ ሙዚቀኞች የሙዚቃ ኮንሰርት ያቀርባሉ፡፡
ከሩሲያ ሴንት ፒተርስቡርግ በመጡ የተለያዩ የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋቾች በሚቀርበው የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ የኢትዮጵያ ታላላቅ ሙዚቀኞች፣ የተለያዩ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት መምህራን፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የሩሲያ ዜጎችና ሩሲያ የተማሩ ኢትዮጵያውያን እንደሚታደሙ ተገልጿል፡፡ ዛሬ በድምቀት ይካሄዳል የተባለው ይህ የሙዚቃ ኮንሰርት፤ የሁለቱን ከተሞች እህትማማችነት ከማጉላቱም በላይ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር የታለመ እንደሆነም የሩሲያ የሳይንስ የባህል ማዕከል የላከው መግለጫ ያመላክታል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና