Sunday, 05 November 2017 00:00

ለሞዛምቢክ ባለስልጣናት በ2ሚ. ዶላር የቅንጦት መኪና መገዛቱ ቁጣ ቀስቅሷል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


    ከፍተኛ የፋይናንስ ችግር ውስጥ የሚገኘው የሞዛምቢክ መንግስት፣ 2 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ የህዝብ ገንዘብ ወጪ በማድረግ አለማቀፍ ብራንድ የሆኑ 45 እጅግ ዘመናዊ የቅንጦት መኪኖችን ለባለስልጣናት ማመላለሻ ለመግዛት ጫፍ ላይ መድረሱንና ይህም የአገሪቱን ዜጎችና የሲቪል ማህበራትን በከፍተኛ ሁኔታ ማስቆጣቱን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት መርሴድስ፣ ቶዮታ ላንድክሩዘር፣ ፎርድ ሬንጀር፣ ሃዩንዳይና ፔጆን ጨምሮ በአለማቀፍ የመኪና ገበያ የላቀ ስም ያላቸው ኩባንያዎች ምርቶች የሆኑ 45 አዳዲስ ሞዴል መኪኖችን ለመግዛት ስምምነት አድርጎ ክፍያ ለመፈጸም እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ የጠቆመው ዘገባው፤ ይህም በማህበራዊ ድረገጾችና በተለያዩ መድረኮች ተቃውሞ እንደገጠመው አመልክቷል፡፡
የመንግስት ባለስልጣናትን ለማንሸራሸር የታሰቡትን እነዚህን የቅንጦት መኪኖች ለመግዛት የተመደበው ገንዘብ፤ በዘንድሮው አመት ለአገሪቱ የአደጋ መቆጣጠር ተቋም ከተያዘው በጀት በእጅጉ እንደሚበልጥና የከተማ ድህነትን ለመቀነስ ከተያዘው በጀት በጥቂቱ እንደሚያንስም ተዘግቧል፡

Read 1887 times