Print this page
Sunday, 29 October 2017 00:00

238 ሴት ተዋንያን፤ ታዋቂውን የሆሊውድ ዳይሬክተር በጾታዊ ትንኮሳ ከሰሱ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የኦስካር እጩው ታዋቂ የሆሊውድ ዳይሬክተርና የፊልም ጸሃፊ ጄምስ ቶባክ፣ ጾታዊ ጥቃትና ወሲባዊ ትንኮሳ አድርሶብናል በሚል በይፋ ክሳቸውን የሚያቀርቡ ሴት ተዋንያን ቁጥር 238 መድረሱን ሎሳንጀለስ ታይምስ ዘግቧል፡፡
ሃርቬ ዊኒስተን የተባለው ታዋቂ የፊልም ፕሮዱዩሰር፣ “ጾታዊ ትንኮሳና የአስገድዶ መድፈር ጥቃት አድርሶብናል” በማለት ከ40 በላይ ሴት ተዋንያን ባለፉት ሳምንታት በአደባባይ ክሳቸውን ማቅረባቸውን ተከትሎ፣ “እኔም” የተሰኘና “ተመሳሳይ ጥቃት ደርሶብኛል” የሚሉ ሴቶች ድርጊቱን ያወገዙበት ዘመቻ፣ በማህበራዊ ድረገጾች ተጧጡፎ መቀጠሉን ያስታወሰው ዘገባው፤በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ደግሞ ሌላኛው ታዋቂ የሆሊውድ ዳይሬክተር ጄምስ ቶባክ፣”ተመሳሳይ ጥቃት ፈጽሞብናል” የሚሉ በርካታ ሴት ተዋንያን ወደ አደባባይ እየወጡ ሲሆን ጉዳዩ ዓለማቀፍ ትኩረት እየሳበ መሆኑንም አስታውቋል፡፡
“ዘ ፒክ አፕ አርቲስት”ን ጨምሮ በርካታ ተወዳጅ ፊልሞችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ዳይሬክተሩ፤በተለይ ጀማሪ ተዋንያንን ወደ ፊልሙ አለም ለማስገባት የተለያዩ ጾታዊ ትንኮሳዎችንና ወሲባዊ ጥቃቶችን እንደሚያደርስባቸው የሚገልጹና “የጥቃቱ ሰለባ ነን” በሚል ምስክርነታቸውን የሚሰጡ የሆሊውድ ሴት ተዋንያን ቁጥር 238 መድረሱን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የ72 አመቱ ዳይሬክተር ከተዋንያኑ የቀረበበትን ክስ፣ “መሰረተ ቢስ ውንጀላ” በማለት ያጣጣለው ሲሆን በእንዲህ አይነት ነውር ላይ ተሰማርቶ እንደማያውቅ መግለጹንም ዘገባው ጠቁሟል፡፡ የፊልም ባለሙያው የጾታ ትንኮሳና ጥቃት ሰለባ ነን በሚል በይፋ ክሳቸውን ካቀረቡት ታዋቂ የሆሊውድ ሴት ተዋንያን መካከል፡- ጁሊያና ሙር፣ ሳሪ ካሚን፣ ስታር ሪናልዲ እና ቴሪ ኮን እንደሚገኙበትም ዘገባዎች ያሳያሉ፡፡

Read 4944 times
Administrator

Latest from Administrator