የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር፣ የአገሪቱ የጦር ሃይል አባላትና ወታደሮች ፌስቡክን ጨምሮ በተለያዩ ማህበራዊ ድረገጾች ላይ ፎቶ ግራፋቸውንና ሌሎች ጽሁፎቻቸውን እንዳይለጥፉ የሚከለክል ህግ እያወጣ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ሚኒስቴሩ ይህንን ህግ ለማውጣት ያነሳሳው፣የደህንነትና የመረጃ ማፈትለክ ስጋት እንደሆነ የጠቆመው ዘገባው፤ ወታደሮቹ የሚለጥፏቸው ፎቶ ግራፎችና ሌሎች ጽሁፎች የት አካባቢና የትኛው የጦር ሰፈር ላይ እንደሚገኙ ለጠላት ሃይል ወታደራዊ መረጃ ሊሰጡ ይችላሉ መባሉን አመልክቷል፡፡ ህጉ ከመጪው ጥር ወር ጀምሮ ተግባራዊ
ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅም የጠቆመው ዘገባው፤ የዩክሬን መከላከያ ሚኒስቴርም በ2015 ላይ በተመሳሳይ ሁኔታ አብዝተው ማህበራዊ
ድረገጽ በሚጠቀሙ ወታደሮቹ ጉዳይ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ገብቶ እንደነበር አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ