Monday, 11 September 2017 00:00

“በእርግጠኝነት መሰለኝ” ሐሙስ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ደራሲ የኑስ በሪሁን ያዘጋጀው “በእርግጠኝነት መለሰኝ” የተሰኘ መፅሀፍ የፊታችን ሁሙስ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በአዜማን ሆቴል ይመረቃል፡፡
በልብ ወለድ አተራረክ ስልት የተቃኘውና ታሪክንና ነባራዊ ሁኔታን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ያለፈውን ከአሁን እያጠቀሰ የሚቃኘው መፅሃፉ፤ መቼቱን በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በሚገኝ ትልቅ ከተማ የትምህርት ተቋም ላይ ያደረገ ሲሆን ሁነቶችን እያሰናሰለ ለውጥ የሚፈጥር መፅሀፍ መሆኑን ደራሲው በመግቢያቸው አስፍሯል፡፡ በ317 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ በ120 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ በምርቃት ስነስርዓቱ በመፅሀፉ ላይ ዳሰሳ የሚካሄድ ሲሆን የተለያዩ ኪነ-ጥበባዊ ዝግጅቶች ይካሄዳሉም ተብሏል፡፡

Read 2092 times