Sunday, 10 September 2017 00:00

“የ21ኛው ክፍለ ዘመን መሳፍንትና ኢትዮጵያን እንደ ሀገር የማስቀጠል ፈተና” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የቀድሞው አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) ከፍተኛ አመራር የነበሩት የኢ/ር ዘለቀ ረዲ፤ “የ21ኛው ክፍለ ዘመን መሳፍንትና ኢትዮጵያን እንደ ሀገር የማስቀጠል ፈተና” የተሰኘ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሃፉ  መሳፍንታዊ አስተሳሰብ ከጥንት ጀምሮ በአገሪቱ ላይ ስላስከተለው ጉዳት፣ አሁን ድረስ የዘለቀው ይህ አስተሳሰብ እንዴት ከፋፍሎ እንደሚገዛ፣ አስተሳሰቡ ህዝቡን ከፋፍሎ ስለሚገዛባቸው መሳሪያዎች፣ በአስተሳሰቡ የትኛው የህብረተሰብ ክፍል ሰለባ እንደሆነና እንዴት ስር ሰዶ አሁን እስካለንበት ዘመን እንደመጣ ይተነትናል፡፡
መሳፍንታዊ አስተሳሰብ አገሪቱን እንደ አገር ለማስቀጠል ምን ያህል ፈተና እንደሆነ የሚገልፀው መፅሃፉ፤ ይህን አስተሳሰብ ከስሩ ለመንቀል የሚያስችሉ የመፍትሄ ሀሳቦችን ይጠቁማል፡፡  በ14 ምዕራፎች  በ236 ገፆች የተመጠነው መፅሀፉ፤ በ75 ብር ከ99 ሳንቲም እና በ28 ዶላር ለገበያ የቀረበ ሲሆን ሎሚ ቡክስ በተባለ የኦላይን የመፅሀፍ ገበያም ጭምር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡

Read 2256 times