Sunday, 10 September 2017 00:00

የሩዋንዳ መንግስት በመዲናዋ የቤት መኪኖች እንዳይንቀሳቀሱ ሊያግድ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  የሩዋንዳ መንግስት በርዕሰ መዲናዋ ኪጋሊ እየተባባሰ የመጣውን የትራፊክ መጨናነቅ ለማስወገድ በማሰብ፣የግለሰቦች የቤት መኪኖች በከተማዋ ጎዳናዎች ላይ እንዳይንቀሳቀሱ የሚከለክል ህግ ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱ ተዘግቧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ከቀጣዩ አመት አጋማሽ ጀምሮ ተግባራዊ ሊያደርገው ያሰበው ይህ ህግ፣ በመዲናዋ ኪጋሊ የህዝብ ትራንስፖርት ከሚሰጡና ከተፈቀደላቸው የተቋማት ተሸከርካሪዎች በስተቀር የግል መኪኖች መንቀሳቀስ አይችሉም ሲል ፐልስላይቭ ከትናንት በስቲያ ዘግቧል፡፡
በከተማዋ ለሚታየው ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ የሚገኙት የግል መኪኖች በመሆናቸው የአገሪቱ መንግስት ህጉን ለማውጣት መገደዱንና የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ አውቶብሱችን በብዛት ወደ ስራ ለማስገባት ማሰቡን ዘገባው አመልክቷል፡፡
ህጉ ጸድቆ ተግባራዊ  ከሆነ፣ የቤት መኪና ያላቸው የኪጋሊ ነዋሪዎች፣ ከ2018 አጋማሽ አንስቶ ብስክሌት ወይም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አውቶብሶችን ለመጠቀም ወይም በእግራቸው ለመጓዝ ይገደዳሉ ተብሏል፡፡

Read 2223 times