Saturday, 02 September 2017 12:37

“አሸንፍጥ” የግጥም መጽሐፍ ነገ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

የገጣሚ አስቻለው አይናለም፣ “አሸንፍጥ” የግጥም ስብስብ መፅሀፍ ነገ ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር ይመረቃል፡፡ በዕለቱ ዶ/ር ሥርግው ገላው በመፅሀፉ ላይ ዳሰሳ ያቀርባሉ፡፡ ከያኔ ስዩም ተፈራ፣ አስቴር በዳኔ፣ መምህር የሻው ተሰማ (የኮተቤው)፣ ዶ/ር ንዋይ ዘርጌ፣ ደራሲ አንተነህ ወንድሙ፣ ገጣምያኑ ሰይፉ ወርቁ፣ መኳንንት፣ መንግስቱ፣ ዮሃንስ ገ/መድህን ኤሊያስ ሽታሁን፣ ብሩክ ሚፍታህ የግጥም ስራዎቻቸውን፤ በመምህር መሰረት አበጀም ዲ ስኩር እ ንደሚቀርብ
ለማወቅ ተ ችሏል፡፡ መድረኩ፣ በጋዜጠኛ ጌታቸው ዓለሙ እንደሚመራና በክራር ተጫዋቹ ታምሩ ንጉሴ ሙዚቃ ዝግጅት ይታጀባል ተብሏል፡፡

Read 2534 times