እናት የማስታወቂያ ድርጅት፣ ከጀርመን የባህል ማዕከልና ከብሄራዊ ቤተ-መጻሕፍትና ቤተ- መዛግብት ኤጀንሲ ጋር በመተባበር፤ ነገ ከቀኑ 8፡ 00 ጀምሮ፣ በሩስያዊው ጸሐፊ አንቷን ቼኮብ ተጽፎ በተርጓሚ ትዕግስት ኅሩይ “ቅብጥብጧ” በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ በተመለሰው መጽሐፍ ላይ፤ በመወዘክር አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡ በዕለቱ፣ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት አቶ ዓለማየሁ አሊ እንደሆኑ የገለፀው እናት የማስታወቂያ ድርጅት፣ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ጋብዟል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና