Sunday, 27 August 2017 00:00

ኢንተርኮንትኔንታል፤ 360 ድግሪ የሚሽከረከር ሬስቶራንቱን ከፈተ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

    ኢንተርኮንትኔንታል አዲስ ሆቴል ያስገነባውና በምሥራቅ አፍሪካ የመጀመሪያው እንደሆነ የተነገረለት 360 ድግሪ የሚሽከረከረው ሬስቶራንት ሰሞኑን አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡
ሆቴሉ በቅርቡ ግንባታውን አጠናቆ አገልግሎት ላይ ያዋለው አዲሱ ሬስቶራንት፣ 360 ድግሪ እየተሽከረከረ ደንበኞች የከተማዋን ዙሪያ እየቃኙ እንዲዝናኑ ለማድረግ ያስችላል ተብሏል፡፡ ሆቴሉ ከትናንት በስቲያ 11ኛ ፎቅ ላይ የሚገኘውን ተሽከርካሪ ሬስቶራንት ለጋዜጠኞች ባስጎበኘበት ወቅት፣ የሆቴሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ይልቃል በቃሉ እንደተናገሩት፣ ተሽከርካሪው ሬስቶራንት በአንድ ጊዜ 120 እንግዶችን ይዞ፣ 360 ድግሪ በመሽከርከር፣ የአዲስ አበባ ከተማን ዙሪያ ያስቃኛል፡፡ ተሽከርካሪው ሬስቶራንት ከተነሳበት ቦታ ተመልሶ ለመድረስ 55 ደቂቃዎች ይወስድበታል ተብሏል፡፡
ሬስቶራንቱ የተለያዩ ሀገራትንና  ባህላዊ የኢትዮጵያ ምግቦችን ለደንበኞቹ ያቀርባል ያሉት ሥራ አሥኪያጁ፤ ደንበኛው ላገኘው አገልግሎት የሚከፍለው ዋጋ ተመጣጣኝ እንደሆነም ገልፀዋል፡፡
በቱሪዝም እንቅስቃሴ ውስጥ ያለውን የገበያ መቀዛቀዝ ችግር መፍትሄ እንደሚያስገኝ እምነት የተጣለበት ስብሰባ፤ የፊታችን ማክሰኞ እዚሁ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እእንደሚካሄድ አቶ ይልቃል በቃሉ ተናግረዋል፡፡
አምና በዚህ ወቅት በአገሪቱ ተከስቶ ከነበረው አለመረጋጋት ጋር ተያይዞ፣ ከፍተኛ የእንግዶች የፕሮግራም ስረዛ ገጥሞን ነበር ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ ዘንድሮ ግን በአንፃራዊ መልኩ የተሻለ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡  

Read 3401 times